



ስለ እኛ
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በመሠረታዊ የፍጆታ ምርት አቅርቦት ገበያን የማረጋጋት፣ ለአምራቹ የገበያ ዕድል መፍጠርንና የውጭ ምንዛሪ ግኝትን በወጪ ንግድ የማሳደግ ተልዕኮዎችን በመወጣት በንግዱ ዘርፍ ከተሠማሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በተመሠረተ መደጋገፍና መተባበር በመሥራት የንግድ ግብይት ሥርዓቱን የተረጋጋ፣ ዘመናዊ፣ አስተማማኝና ውጤታማ ለማድረግና ተወዳዳሪ ተቋም ሆኖ ለመገኘት የሚሠራ የመንግሥት የልማት ተቋም ነው፡፡
ራዕያችን
በ2025 በአፍሪካ ተወዳዳሪ፣ ተመራጭና ተደራሽ የንግድ ተቋም ሆኖ መገኘት
ተልዕኳችን
ጥራታቸውን የጠበቁና የተመረጡ የግብርናና የኢንደስትሪ ምርቶች ከሀገር ውስጥና ከውጭ በጥራት በመግዛት ለተጠቃሚው ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ፣ ለአርሶ አደሩና አምራቹ የገበያ ዕድል በመፍጠር፣ የግብርናና የኢንደስትሪ ምርቶች ወደ ውጭ ገበያ በመላክ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን በማሳደግ፣ የሎጂስቲክስ፣ ቴክኒክና ሌሎች ተጓዳኝ አገልግሎቶችን በማቅረብ እንዲሁም የቴክኖሎጂና የሰው ሃብት ልማትን በማሳደግ በሀገራችን ቀልጣፋና ዘመናዊ የንግድ ሥርዓት እንዲስፋፋና ለኤኮኖሚ ዕድገት መፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማድረግ፡፡
ምርትና አገልግሎት
ተጓዳኝ አገልግሎቶች
የትራንስፖርት፣ የተሽከርካሪ ጥገናና ማሽንሾፕ፣ እህል ብጠራ፣ የምድር ሚዛን፣ የቡናና ቅባት እህሎች ብጠራና ማደራጀት፣ የቡና ቀመሳና ሌሎችም ተጓዳኝ አገልግሎቶች
ዜና
በምርት አቅራቢነት ከኮርፖሬሽኑ ጋር መሥራት ይፈልጋሉ?
በመሠረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ወይም በኢንዱስትሪ ውጤቶች ማምረት ሥራ ላይ ተሠማርተዋል? እንግዲያውስ የምርትዎን ተደራሽነት በማስፋት ተጠቃሚነትዎን ያሳድጉ! በአቅራቢነት ለመመዝገብ “ይመዝገቡ” የሚለውን አዝራር ይጫኑ፡፡
በመደብሮቻችን
በሣምንቱ ለተጠቃሚዎች የቀረቡ የአትክልት፣ የፍራፍሬና በፋብሪካ የተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች
ከደንበኞቻችን አንደበት
