Harbour

 

በዓለም አቀፍም ሆነ በአገራዊ የንግድ እንቅሰቃሴ ውስጥ በተለይም ምጣኔ ኃብትን የሚያንቀሳቅሱና የንግድ ሥርዓቱ አካላትና ማኅበረሰቡ ተሣታፊ በሆኑበት የንግድ ሥራ ውስጥ የተደራጀና ሥራዎችን በቀላጠፈ አኳኋን ለማስኬድ የሚያስቸል የሎጂስቲክስ አገልግሎት ለአገልግሎት ሰጪው የጀርባ አጥንት ነው፡፡ በዚህ ረገድ ኢንሥኮ የሚያካሄዳቸው ምርት ተኮር የሆኑ የንግድ እንቅስቃሴዎች በምርት በአገር አቀፍ ደረጃ በሚከናወኑ የምርቶች ግብይትና ዝውውር ላይ የተመረከዙ እንደመሆናቸው ለዚሁ አገልግሎት የሚውሉ ተሸከርካሪዎች መኖርና በአግባቡ ሥራ ላይ መዋል መሠረታዊ ነው፡፡ አገልግሎቱ የምርት ግዢና ሽያጭ ሥራዎችን በማቀላጠፍ ተገቢውን አገልግሎት በተገቢው ጊዜ እንዲሠጥ ያስችላል፡፡

 

ለዚሁ አገልግሎት መሳለጥም ለተሸከርካሪዎች መደበኛና የተሟላ ጥገና ማድረግ የሚያስችል የመሣሪያና የጥገና ማዕከል ያስፈልጋል፡፡ በኮርፖሬሽኑ የእህልና ቡና ማደራጃ ማዕከል የሚገኘው የሎጂስቲክስ አገልግሎት የሥራ ክፍል ይህን አገለግሎት ለበርካታ ዓመታት ሲሰጥ ቆይቷል፤ እየሰጠም ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ የአገልግሎት አንድ አካል የሆነው የተሸከርካሪዎች ጥገናና እንክብካቤ አገልግሎቶች ሲሰጡባቸው የነበሩ አውታሮች ከኮርፖሬሽኑ የንግድ ሥራዎች ስፋትና አቅም ተመጣጣኝ ሳይሆኑ በመቆየታቸው ለባለሙያዎችና የሥራ አፈጻጸም ማነቆ ሆኖ ቆይቷል፡፡ በተለይም ጥገናዎች የሚናወኑበት ደረጃውን የጥገና ማዕከል ባለመኖሩ የቴክኒክ ባለሙያዎች ጸሐይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው መሣሪዎችም ለብልሽት ተጋላጭ ሆነው አገልግሎቱ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

 

ይህን ማነቆ ለመፍታትና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል ኮርፖሬሽኑ በቅርቡ በወሰደው እርምጃ ለባለሙያዎችና ለተቀላጠፈ አሠራር በሚያመች መልኩ የአዳዲስና ዘመናዊ ጥና ማዕከሎች ግንባታ ተጀምሮ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታው በአንድ ጊዜ ለ17 ተሸከርካሪዎች አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሲሆን ባለሙያዎችም በማንኘውም የአየር ሁኔታ ሥራቸውን ማከናወን የሚችሉበት ነው፡፡