ስለ እኛ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን ባወጣው አዋጅ ቁጥር 916/2008 አንቀጽ 5 መሠረት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 369/2008 ታኅሳስ 12 ቀን 2008 ዓ/ም የተቋቋመ የፌዴራል መንግሥት የልማት ድርጅት ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ በተናጠል ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን የኢትዮጵያ የእህል ንግድ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ድርጅት፣ የኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ገበያ አክስዮን ማህበር እና የግዥ አገልግሎት ድርጅትን በማቀፍ በንግዱ ዘርፍ ከተሠማሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በተመሠረተ መደጋገፍና መተባበር በመሥራት የንግድ ግብይት ሥርዓቱን የተረጋጋ፣ ዘመናዊ፣ አስተማማኝና ውጤታማ ለማድረግና ተወዳዳሪ ተቋም ሆኖ ለመገኘት የሚሠራ የመንግሥት የልማት ተቋም ነው፡፡ |
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከኩሽላደር ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር የህንጻ ሙሉ እድሳት (ሪኖቬሽን) የውል ስምምነት ግንቦት 15 ቀን 2016 ዓ/ም አደረገ፡፡ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ...
ኮርፖሬሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተለያዩ ገበያ የማረጋጋት ተግባራትን አከናውኗል፡፡ ከእነዚህም ዋና ዋናዎቹ፡- ለአምራቹ ምርት ገበያ መፍጠር ለአርሶ አደሩ ምርት የገበያ ዕድል በመፍጠር ረገድ፡- የአርሶ አደሩን ምርታማነት በቀጣይነት ለመደገፍ ኮርፖሬሽኑ 1,088,387...
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከካይዘን ልህቀት ማዕከል ጋር የካይዘን ፕሮጀክት ትግበራ የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ ሥነ-ሥርዓት መጋቢት 02/ 2016 ዓ.ም አካሄደ፡፡ የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን አቶ አቻ ደምሴ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን...
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽንን ያለፉት ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ጥር 8/ 2016 ዓ.ም በአካል ተገኝተው ግምገማ አካሄዱ፡፡ የቋሚ ኮሚቴው...
ኮርፖሬሽኑ በሀገራችን ከህዳር 16 እስከ ታህሣሥ 1 ቀን 2016 ዓ.ም የተከበሩት ዓለም አቀፍ የኤድስ ቀን እና የፀረ ጾታዊ ጥቃት (የነጭ ሪባን) ቀንን በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ታህሳስ 20/ 2016 ዓ.ም አከበረ፡፡...
የምርት ጥራት ቁጥጥርና ክምችት እንክብካቤ መመሪያ ላይ ከኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤትና ዘርፎች ለተውጣጡ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ዓላማ ኮርፖሬሽኑ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የጥራት ቁጥጥር ስራን ስርዓት...