በኮርፖሬሽን ደረጃ ወጥነት ያለው የመረጃ አደረጃጀትና ሥርጭትን በመጠቀም ለደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የውስጥ መረጃ ልውውጦችንም ቀልጣፋና የተሟላ ለማድረግ በሚቻልበት አሠራር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ነሀሴ 18 ቀን 2012 ዓ/ም በኮርፖሬሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡

በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ በተሰጠው ሥልጠና የኮርፖሬሽኑ ም/ዋና የሥራ አስፈጻሚዎች፣ የዘርፍ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ከፍተኛና መካከለኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ የጽሕፈት ሥራና የቢሮ ውበት አስተዳደር ባለሙያዎች እንዲሁም የሪከርድና ማህደር ባለሙያዎች ተሣትፈዋል፡፡

ዓላማው የመረጃ አያያዝና አሰረጫጨትን በካይዘን ፍልስፍና በመታገዝ መረጃዎችን በቀላሉ ማግኘት ፣በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂን በመታገዝ የደብዳቤዎች ምልልስን በማስቀረት ግዜን እና ጉልበትን ከብክነት ማዳን የሚያስችሉ አሰራሮችን ማመላከት በሆነው ስልጠና መነሻነት የተለያዩ ውይይቶች ተደርገዋል፡፡

በሥልጠናው ማጠቃለያ በኮርፖሬሽን ደረጃ ወጥ የሆነ መረጃ አደረጃጀት እንዲኖር በሙያው የሚመለከታቸውን ባለሙያዎች ያቀፈ የመመሪያ ዝግጅት ኮሚቴ እንዲዋቀር ቀደም ብሎ ለመረጃ አያያዝ በግብዓትነት የተጠየቁ በተቻለ አቅም ግዥ እየተፈጸም እንዲቀርብ በሚመለከታቸው አካላት ትኩረት እንዲሰጥ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡