የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራር እና ሠራተኞች ታህሳስ 12 ቀን 2014 ዓ/ም በኮርፖሬሽኑ ዋና መስሪያ ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የደም ልገሳ እና በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተለያዩ ቁሳቁሶችን የማሰባሰብ መርኃ ግብር አካሄዱ፡፡

በኮርፖሬት የማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት አስተባባሪነት ከኮርፖሬሽኑ አመራር እና ሠራተኞች የተሰባሰቡት አልባሳት፣ የህጻናትና የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ ምርቶች፣ የልጆች ወተት እና የታሸጉ ምግቦች መሆናቸውን የገለጹት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት በጅጋ፤ ኮርፖሬሽኑ ለሀገር መከላከያ ሠራዊትና በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ግንባር ድረስ በመሄድ ለማስረከብ በጥቅሉ የሶስት ሚሊየን ብር ድጋፍ በገንዘብና በዓይነት ማዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡

 

002a.JPG

 

002b.JPG