Firdu.JPG

የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን አመራርና ሠራተኞች በኮርፖሬሽኑ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ በክልልና በአዲስ አበባ ከሚገኙ የኮርፖሬሽኑ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች የተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኙበት ጎተራ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የስብሰባ አዳራሽ መጋቢት 8 ቀን 2014 በተካሄደው ውይይት ላይ የ2014 የመጀመሪያ 6 ወራት የሥራ አፈጸጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ በወቅቱ በመተመዘገቡ አበረታች ክንውኖችና መስተካከል በሚገባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡

በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊከዋናወኑ በሚገባቸው ጉዳዮች ዙሪያ በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ በኦፕሬሽን ሥራዎች፣ ትርፋማነትን በሚያጎለብቱ አሠራሮች፣ በወጪ ቀቅነሳ፣ በቅንጅታዊ አቅም ግንባታ፣ በግንዛቤ ፈጠራና በሌሎችም አንኳር ጉዳዮች ዙሪያ መከናውን ስለሚገባቸው ተግባራት አቅጣጫዎች ተቀምጠ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

በሌላም በኩል በ2013 ዓ/ም በዕቅድ አፈጻጸም እና በለውጥ ሥራዎች የላቀ አፈጻጸም ላከናወኑ የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች የዕውቅናና ሽልማት መርኃ ግብር መጋቢት 9 ቀን 2014 ዓ/ም በጎተራ የስብሰባ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ በመርኃ ግብሩ ላይ የኢንሥኮ ሥራ አመራር ቦርድ፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታ አስተዳደር እና የኮርፖሬሽኑ አመራር አባላት የተገኙ ሲሆን፤ በበጀት ዓመቱ በዕቅድ አፈጻጸምና የለውጥ ሥራዎች የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ሠራተኞች፣ ቡድኖችና የንግድ ሥራ ዘርፍ የዕውቅና ሰርቲፊኬት ከገንዘብና ዓይነት ሽልማቶች ጋር ተበርክቶላቸዋል፡፡ የዕውቅናና ሽልማት መርኃ ግብሩ የላቀ አፈጻጸም ያላቸውን ፈጻሚዎች ለላቀ አፈጻጸም ለማነሳሳትና ሌሎችም የእነርሱን ፈለግ በመከተል የሥራ አፈጻጸማቸውን እንዲያጎለብቱ ጉልህ አስተዋጽዖ እንዳለው ተሸላሚዎችና የሥነ ሥርዓቱ ተሣታፊዎች ገልፀዋል፡፡