Training_2.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽንን በቅርቡ ለተቀላቀሉ አዲስ ሰራተኞች የትውውቅ ስልጠና ታህሳስ 13 ቀን 2015 ዓ/ም ተካሄደ፡፡ ስልጠናውን ያዘጋጀው የኮርፖሬት የሰው ሃብት ልማትና ሥራ አፈጸጻም አመራር ቡድን ሲሆን የስልጠናው ዓላማ ለአዲስ ሰራተኞች የኮርፖሬሽኑን አጠቃላይ ገጽታ እና አሰራር ማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

በኮርፖሬሽኑ የሰው ሃብት ልማትና ሥራ አፈጸጻም አመራር ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ይመር አዲስ ሰራተኞች ኮርፖሬሽኑን ሲቀላቀሉ ስለድርጅቱ አወቃቀር፣ የሥራ ሂደት እንዲሁም ከሥራ ባልደረቦች ጋር የማስተዋወቅ ስራ እንደሚሰራ ገልጸው በዚህም መሰረት የዛሬው ስልጠና መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡

አቶ ምክረ ተክሌ፣ ከፍተኛ የሰው ሃብት ባለሙያ በኮርፖሬሽኑ የህብረት ስምምነትና በሃብት አመራር መመሪያ ላይ የተቀመጡ የሰራተኞች መብትና ግዴታዎችን ለአዲስ ሰራተኞች ያብራሩ ሲሆን አዲስ ሰራተኞች በመመሪያ የተደገፉ መብትና ግዴታቸውን አውቀው መስራት እንደሚገባቸውና በተቻለ መጠን የሥራ ዲሲፕሊን ጠብቀው መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡