02.jpg

 

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከየካቲት 16-20/2015 ዓ.ም "የወጪ ንግድ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል እያካሄደ ባለው ዓውደ ርዕይ ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡

ዓውደ ርዕዩ የአገራችንን የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶችን በአጠቃላይ ለአገር ውስጥና ከውጭ ሃገራት ተሳታፊ ለሚሆኑ ጎብኝዎች ማስተዋወቅን ዓላማው አድርጓል፡፡ በዓውደ ርዕዩ ላይ የሃገር ውስጥና የውጭ ሃገራት አምራቾች በመሳተፍና ግብይት በማካሄድ ላይ ናቸው፡፡

ኮርፖሬሽኑ ለገበያ የሚያቀርባቸው ጥራታቸውን የጠበቁ የቡና፣ የቅባት እህል፣ የጥራጥሬና ቅመማ ቅመም ምርቶች፣ ልዩ ልዩ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩና የግብርና መሠረታዊ ምርቶችን፣ ለህብረተሰቡ ፍጆታ የሚውሉ መሠረታዊ የምግብን የንጽሕና መጠበቂያ ሸቀጦችና ሌሎችንም ምርቶቹን በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡

01.jpg03.jpg

 

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና ድረገጻችን በመጎብኘት የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ!

ድረገጽ፡- https://www.etbc-ethiopia.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo
ዜና ኢንሥኮ አንድሮይድ መተግበሪያ፡- https://t.ly/DiXR
ዩትዩብ ቻነል፡- https://www.youtube.com/@etbcinfocom4858

አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ያድርሱን፡፡
ኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት