Trucks.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሚያከናውናቸውን የግብይት ሥራዎች ለማሳለጥ የሚያገለግሉ ተጨማሪ አራት ከባድ ተሽከርካሪዎች ግዢ አከናወነ፡፡ የተሽከርካሪ ርክክቡ በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት በተከናወነበት ወቅት አንደተገለጸው የተገዙት ተሽከርካሪዎች እያንዳንዳቸው 50 ኩንታል፣ በድምሩ 200 ኩንታል የመጫን አቅም ያላቸው ሲሆን በአጠቃላይ ከ11.4 ሚሊየን ብር ወጪ ተደርጎባቸው ኢትዮ ኒፖን ከተባለው ኩባንያ የተገዙ ናቸው፡፡