report.jpg

ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት ባለፉት ሰባት ወራት በሀገር ውስጥና በውጭ ገበያ ለመሸጥ ካቀደው 2.29 ሚሊዮን ኩንታል የእህልና ቡና፣ የፍጆታ ዕቃ እና የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርት 2.27 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ወይም የዕቅዱን 99 በመቶ ለገበያ አቀረበ፡፡ በተለይም በሀገር ውስጥ ለመሸጥ ያቀዳቸዉ ልዩ ልዩ ሸቀጦች መጠን 1.69 ሚሊዮን ኩንታል ሲሆን በዚህ ወቅት መሸጥ የተቻለው 2.05 ሚሊዮን ኩንታል ወይም የዕቅዱን 107 በመቶ እንደሆነ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡

በሌላ በኩል ኮርፖሬሽኑ 1.23 ሚሊዮን ኩንታል እህልና ቡና፣ አትክልትና ፍራፍሬ እና ፍጆታ ዕቃዎች ከሀገር ውስጥ አምራቾች ለመግዛት አቅዶ 944 ሺህ ኩንታል በመግዛት የዕቅዱን 77 በመቶ ማከናወን እንደተቻለ የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ ያሳያል፡፡

ኮርፖሬሽኑ የአቅርቦትና የግብይት ችግር የሚስተዋልባቸውና በአጭር ጊዜ የሚበላሹ የግብርና ምርቶች በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 211 የመገበያያ ማዕከላት ምርቶችን ከአምራቹ በቀጥታ በመግዛት ለሸማቹ እያቀረበ ይገኛል፡፡ እስከ 900 ኪሎሜትር ርቀት በመጓዝ ከፍተኛ የግብርና ምርት ከሚመረትባቸው አካባቢዎች ለአምራቹ ተገቢውን ዋጋ ሰጥቶ በመግዛት የምርት እጥረት ወደ አለባቸው አካባቢዎች በማጓጓዝ በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ ያቀርባል፡፡ ይህም በመደረጉ አምራቾች በገበያ እጥረት ምክንያት ምርታቸው እንዳይበላሽና ባመረቱት ምርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ትልቅ ድጋፍ አድርጓል፡፡ ሸማቹ ህብረተሰብንም ከመደበኛ ገበያው የዋጋ ቅናሽ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡

 

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና ድረገጻችን በመጎብኘት የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ!

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo
ዜና ኢንሥኮ አንድሮይድ መተግበሪያ፡- https://t.ly/DiXR
ዩትዩብ ቻነል፡- https://www.youtube.com/@etbcinfocom4858

አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ያድርሱን፡፡

ኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት