Web.JPG
 
  
ከኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋናው መ/ቤት፣ ዘርፎችና የክልል ግብይት ማዕከላት የተውጣጡ ሠራተኞች “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን አረንጓዴ ዐሻራ የማኖርና በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዘመቻ መሠረት በማድረግ ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ/ም በቢሾፍቱና በክልል ከተሞች የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር አካሄዱ፡፡
 
“የህብረተሰብ አጋርነታችንን በአረንጓዴ አሻራችን እናጎለብታለን” በሚል መሪ ቃል የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሠራተኞች ቢሾፍቱ በሚገኘው የአዳማ ግብይት ጣቢያ በኮርፖሬሽን ደረጃ በተካሄደው የተከላ መርኃ ግብር ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ የችግኝ ተከላው ለአካባቢ ደኅንነትና ጥበቃ እንዲሁም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ረገድ ሁሉም የራሱን አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሚገባውን አጽንዖት ሰጥተዋል፡፡
 
መሠል የተከላ መርኃ ግብሮችን በየዓመቱ ማካሄድ ባህል በሆነበት በኮርፖሬሽኑ ዘንድሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ 28 የኮርፖሬሽኑ የግብይት ማዕከላት በአጠቃላይ 7ሺህ 423 የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓዬ፣ የሎሚ፣ የሙዝ እና የቡና ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 784 አመራርና ሠራተኞች ተሣትፈዋል፡፡
 

ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡