የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፓሬሽን
Ethiopian Trading Businesses Corporation
Toggle navigation
መነሻ ገጽ
ሰለ እኛ
አመሠራረት
ድርጅታዊ መዋቅር
ራዕይና ተልዕኮ
ምርትና አገልግሎት
እህልና ቡና
አትክልትና ፍራፍሬ
የፍጆታ ዕቃዎች
ግዢና ማማከር
ማስታወቂያዎች
ጨረታ
ክፍት የሥራ ቦታ
የግዢና ማማከር ሥልጠና ፕሮግራም
ለገበያ የቀረቡ ምርቶች
ግብረ መልስ
ሚዲያ
ዜና
የፕሬስ መግለጫ
ሰነዶች
ዓውደ ምስል
ኢንሥኮ በሚዲያ እይታ
አድራሻ
የሥራ አስፈጻሚዎች አድራሻ
የኮርፖሬሽኑና የሥራ ዘርፎች አድራሻ
ግብረ መልስ
የዋና ሥራ አስፈጻሚው መልዕክት
Downloads
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ሠራተኞች የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር አካሄዱ
ከኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋናው መ/ቤት፣ ዘርፎችና የክልል ግብይት ማዕከላት የተውጣጡ ሠራተኞች “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን አረንጓዴ ዐሻራ የማኖርና በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል ዘመቻ መሠረት በማድረግ ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ/ም በቢሾፍቱና በክልል ከተሞች የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር አካሄዱ፡፡
“የህብረተሰብ አጋርነታችንን በአረንጓዴ አሻራችን እናጎለብታለን” በሚል መሪ ቃል የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሠራተኞች ቢሾፍቱ በሚገኘው የአዳማ ግብይት ጣቢያ በኮርፖሬሽን ደረጃ በተካሄደው የተከላ መርኃ ግብር ላይ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ የችግኝ ተከላው ለአካባቢ ደኅንነትና ጥበቃ እንዲሁም
የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያለው መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ረገድ ሁሉም የራሱን አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሚገባውን አጽንዖት ሰጥተዋል፡፡
መሠል የተከላ መርኃ ግብሮችን በየዓመቱ ማካሄድ ባህል በሆነበት በኮርፖሬሽኑ ዘንድሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ 28 የኮርፖሬሽኑ የግብይት ማዕከላት በአጠቃላይ 7ሺህ 423 የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓዬ፣ የሎሚ፣ የሙዝ እና የቡና ችግኞች የተተከሉ ሲሆን 784 አመራርና ሠራተኞች ተሣትፈዋል፡፡
ተጨማሪ ምስሎችን ለማየት
እዚህ
ይጫኑ፡፡