NewYearProducts.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለመጪው የ2016 ዓ/ም አዲስ ዓመት በዓል የሚሆኑ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ለገበያ ካቀረባቸው ምርቶች መካከል የዳቦ ዱቄት (ባለ 10 እና 50 ኪ/ግ)፣ ፓልም የምግብ ዘይት (ባለ 3፣ 5 እና 20 ሊትር)፣ ፈሳሽ ዘይት፣ ሽንኩርት እና ቲማቲም ይገኙበታል፡፡

 

ኮርፖሬሽኑ እነዚህን ምርቶች በስሩ በሚገኙት የፍጆታ ዕቃዎች ሽያጭ ማዕከላትና በአትክልትና ፍራፍሬ ማከፋፈያ ሱቆች በማቅረብ ላይ የሚገኝ ሲሆን ለተማሪዎች መማሪያ የሚውሉ ባለ 32፣ 50 እና 100 ቅጠል ደብተሮችን በቀጣይ ቀናት ለገበያ ያቀርባል፡፡