ExcerciseBook800.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለተማሪዎች መማሪያ የሚውል ከሶስት ሚሊየን በላይ መማሪያ ደብተር ከውጭ ሃገር በማስገባት በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡

ለገበያ የቀረበው ደብተር ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ፣ በቀላሉ ውሃ የማያስገባ (water proof) ጠንካራ ሽፋን (double cover) ያለው ሲሆን ዋጋው ለአዲስ አበባ በችርቻሮ 48 ብር እና በጅምላ ደግሞ 50 ብር ሲሆን ለክልሎች መጠነኛ የትራንስፖርት ታሪፍ ተጨምሮ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡ ህብረተሰቡ ደብተሮቹን በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ ንግድ ስራ ዘርፍ መደብሮች፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ስራ ዘርፍ ማከፋፈያዎችና የእህልና ቡና ንግድ ስራ ዘርፍ ማእከላት ማግኘት ይችላል፡፡