የኮርፖሬሽኑ አመራርና ሰራተኞች የፌዴራል ፖሊስ አባላት በተገኙበት ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ጥቅምት 5/ 2016 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡30 በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ሰንደቅ ዓላማ የመስቀል ስነ-ስርዓት በማካሄድና የኢትዮጵያን ብሄራዊ የህዝብ መዝሙር በመዘመር አከበሩ፡፡

የዘንድሮው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን "የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው" በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡

በኮርፖሬሽኑ የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ወ/ሮ እቴነሽ ገ/ሚካኤል ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀንን አስመልክተው ባደረጉት አጭር ገለጻ አገራችን ኢትዮጵያ ከቅኝ ገዥ ወራሪዎች ድንበሯን ተከላክላ፤ ነፃነቷን አስከብራ የኖረች የጥቁር ሀገሮች መመኪያ መሆኗን አስታውሰዋል፡፡

አያይዘውም የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ ሦስትን መነሻ በማድረግ የወጣው የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 በየዓመቱ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን እንዲከበር መደንገጉንና በዚህም መሠረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ/ም በዓሉ በየዓመቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ በጥቅምት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ሰኞ ቀን እንዲከበር መወሰኑን ጠቅሰዋል።

 

 

 

 

ተጨማሪ ምስሎችን እዚህ ይመልከቱ፡፡