photo_2023-12-15_11-37-55.jpg

 

የኮርፖሬሽኑ ንብረት በአግባቡ እንዲታወቅ ለማስቻል የቋሚ ንብረት መለያ ኮድ አሰጣጥ መመሪያ ተዘጋጅቶ ለማኔጅመንት ቀርቦ ጸድቋል፡፡ የጸደቀውን መመሪያ አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ከዋናው መሥሪያ ቤትና ከሁሉም ዘርፎች ለተውጣጡ የንብረትና ፋይናንስ ሠራተኞች ተሰጠ፡፡

የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናውን ያስጀመሩት የኮርፖሬሽኑ የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተሠራ ተገኘወርቅ እንደገለጹት እንደ ኮርፖሬሽን የንብረት መለያ ኮድ መስጠት በማስፈለጉ መመሪያ መዘጋጀቱን ጠቅሰው፤ ሥልጠናው የተዘጋጀው በመመሪያው ዙሪያ ግንዛቤ ለመፍጠር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የቋሚ ንብረት መለያ ኮድ አሰጣጥ መመሪያው አራት ክፍሎች ያሉት ሲሆን ከዓላማዎቹ መካከል ንብረትን ከብክነት መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም ንብረትን በቀላሉ ለማስተዳደር ማስቻል የሚሉት ይገኙበታል፡፡