የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ዋና ከተማ ጅግጅጋ የገበያ ማዕከል በደረሰው ቃጠሎ ለተጎዱ ወገኞች ማቋቋሚያ የሚሆን የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ/ም አደረገ፡፡ በኮርፖሬሽኑ የኮርፖሬት ህ/ማህ/ጉ/አሰ/ማሻ/ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ይርጋሸዋ ተሾመ ለኢንጂነር ዚያድ አብዲ የጅግጅጋ ከተማ ከንቲባና የዕርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ አባላት ድጋፉን ያስረከቡ ሲሆን በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደተናገሩት ኮርፖሬሽኑ ይህንን ድጋፍ ያበረከተው የህዝብ አለኝታነቱንና ወገናዊነቱን ለማሳየት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

12.jpg