የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ያዘጋጀው 14ኛው የአዲስ ቻምበር ዓለም አቀፍ የእርሻና ምግብ ንግድ ትርኢት ከህዳር 27 -29 /2016 ዓ/ም በሚሊኒየም አዳራሽ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በንግድ ትርኢቱ ላይ በመሳተፍ ጥራታቸውን የጠበቁና በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ የሚያቀርባቸውን ናሙና የእህልና ቡና ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች እና የፍጆታ ሸቀጦችን ለጎብኚዎች አስተዋውቋል፤ ከአምራች ድርጅቶች ጋር የገበያ ትስስር መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

የኮርፖሬሽኑ የበላይ አመራሮችም የንግድ ትርኢቱን በቦታው ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡

 

6a.jpg