በኮርፖሬሽኑ የግዢ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ከዋና መ/ቤትና ከሁሉም ዘርፎች ለተውጣጡ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ታህሳስ 8/ 2016 ዓ/ም ተሰጠ፡፡


በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የህግ፣ ማህ/ጉ/አሰ/ማሻ/ም/ዋ/ሥ/አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ይርጋሸዋ ተሾመ ኮርፖሬሽኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ ስራው እየሰፋ በመምጣቱ አሰራሩ በመመሪያ እንዲታገዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ መመሪያዎች በትክክል ስራ ላይ መዋላቸውን መከታተል፣ በአፈጻጸም ያጋጠሙ ችግሮችን በየጊዜው መመዝገብ እና በየደረጃው ላለ አካል ማሳወቅ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ አክለውም ስልጠናው ወጥ የሆነ ግንዛቤ ይዞ ወደ ስራ ለመግባት የሚያስችል ዓላማ ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የግዢ መመሪያው ሲዘጋጅ ነባሩ የግዢ መመሪያ፣ የመንግስት የግዢ መመሪያዎች እንዲሁም የሌሎች ተቋማት የግዢ መመሪያዎቸ በግብአትነት መወሰዳቸው ተመልክቷል፡፡ የግዢ አፈጻጸም መመሪያው ዘጠኝ ምእራፎች ያሉት ሲሆን ከያዛቸው ዓላማዎች መካከል አንድ ወጥ የሆነ የግዢ አፈጻጸም ስርዓት በመዘርጋት የኮርፖሬሽኑን የአሰራር ሂደት ግልጽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ማድረግ ነው፡፡

5.jpg