የምርት ጥራት ቁጥጥርና ክምችት እንክብካቤ መመሪያ ላይ ከኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤትና ዘርፎች ለተውጣጡ ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡


የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ዓላማ ኮርፖሬሽኑ የተቋቋመበትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የጥራት ቁጥጥር ስራን ስርዓት ባለዉና በተቀናጀ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ ደንበኛን ለማርካትና የኮርፖሬሽኑን ትርፋማነት ለማረጋገጥ መሆኑን ስልጠናውን የሰጡት በኮርፖሬሽኑ የምርት ጥራት፣ ቁጥጥርና ክምችት እንክብካቤ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ደመቀ ሰውነት አብራርተዋል፡፡


መመሪያው ሲዘጋጅ ሰነዶችን መነሻ በማድረግ፣ መረጃ በመሰብሰብና ትንታኔ በመስራት ያሉትን መልካም ተሞክሮዎችን እንዲሁም ክፍተቶችን በመለየት ተያያዥነት ያላቸዉን የመንግስትና የህግ ድንጋጌዎ፣ ሀገር-አቀፍና አለም-አቀፍ ደረጃዎችንና ስምምነቶችን፣ መልካም ተሞክሮዎችን ወ.ዘ.ተ ታሳቢ መደረጉን አቶ ደመቀ ገልጸዋል፡፡

 

 

 2.jpg