ኮርፖሬሽኑ በሀገራችን ከህዳር 16 እስከ ታህሣሥ 1 ቀን 2016 ዓ.ም የተከበሩት ዓለም አቀፍ የኤድስ ቀን እና የፀረ ጾታዊ ጥቃት (የነጭ ሪባን) ቀንን በተለያዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ታህሳስ 20/ 2016 ዓ.ም አከበረ፡፡

 

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የኮርፖሬት የሕግ፣ ማህበራዊ ጉዳዮችና አሠራር ማሻሻያ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ይርጋሸዋ ተሾመ አለም አቀፍ የኤድስ ቀን እና የፀረ ጾታዊ ጥቃት (የነጭ ሪቫን) ቀን በየዓመቱ የምናከብረው ለበአልነት ብቻ ሳይሆን ግንዛቤ ለመፍጠር በማሰብ ነው በማለት ሴቶችን ከማንኛውም ጥቃት መከላከል እንደሚገባ እንዲሁም ችላ እየተባለ የመጣው የኤችአይቪ ቫይረስ (ኤድስ) ልዩ ትኩረት እንደሚያስፈልገው በመጥቀስ የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞች ጤናቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም በኮርፖሬሽኑ ሲካሄድ የቆየው ስፖርታዊ ውድድር ለአንድ ዓላማና ለአንድ ግብ በጋራ የመስራት የኮርፖሬት መንፈስን ለመፍጠር እንደተዘጋጀ ጠቁመው አንድ ጠንካራ የእግር ኳስ ቡድን በመመስረት በቀጣይ ከሌሎች ተቋማት ጋር ውድድር እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

 

በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስር በሚገኙት ንግድ ሥራ ዘርፎችና ዋናው መ/ቤት መካከል ለወራት ሲደረግ የነበረው የእግር ኳስ ውድድር ሲጠናቀቅ የፍጆታ እቃዎች ን/ሥ/ ዘርፍ (አለ በጅምላ) እግር ኳስ ቡድን የዋንጫ ባለቤት ሆኗል፡፡ በፍጻሜ ጨዋታ የፍጆታ እቃዎች ን/ሥ/ ዘርፍ የእህልና ቡና ን/ሥ/ ዘርፍን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ዋንጫውንም ከኮርፖሬት የሕግ፣ ማህበራዊ ጉዳዮችና አሠራር ማሻሻያ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ይርጋሸዋ ተሾመ እጅ በመቀበል ከደጋፊዎቻቸው ጋር በልዩ ህብረ ዝማሬ በመታገዝ ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ በውድድሩ ሁለተኛ በመውጣት ጥሩ ተፎፎካሪ ለነበረው የእህልና ቡናን/ሥ/ ዘርፍ የእግር ኳስ ቡድን የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡

 

ከእግር ኳስ ውድድሩ ጎን ለጎን በሴት ሰራተኞች መካከል የሩጫ ውድድር የተካሄደ ሲሆን የማታወርቅ ንጉሴ ከዋና መ/ቤት በአንደኝነት ውድድሩን ያጠናቀቀች ሲሆን ከአንድ እስከ ሶስት ለወጡ ተወዳዳሪዎችና ለአንድ ልዩ ተወዳዳሪ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

 

01.jpg 02.jpg

 

03.jpg 04.jpg

 

05.jpg