ከግንቦት 1-5/2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሔደው 12ኛው አዲስ ቻምበር የእርሻና ምግብ አለም አቀፍ ንግድ ትርኢት ከተለያዩ ዘርፎች ልዩልዩ ምርቶችን በማስተዋወቅ ለተከታታይ 5 ቀናት በተካሔደው ንግድ ትርኢት ላይ የኢትጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ተሳትፏል፡፡

ይህም የኮርፖሬሽኑ ዘርፎች ለሚያቀርቡት ምርትና አገልግሎት ከደንበኞች እና ከአቅራቢዎች ጋር ለመገናኘት መልካም አጋጣሚ ነው፡፡የውጭና የአገር ዉስጥ ደንበኞችን አመለካከት በማሻሻል ረገድም ንግድ ትርኢቱ ሚናው የጎላ መሆኑ ታምኖበታል፡ ከሁሉም በላይ ግን ኮርፖሬሽኑ በህዝብ ዘንድ እውቅና እንዲፈጠርለት ከማድረግ አኳያ ንግድ ትርኢቱ ተኪ የሌለው ሚና ይጫወታል፡፡

በንግድ ትርኢቱ ከእህልና ቡና ንግድ ሥራ ዘርፍ፣ ከፍጆታ እቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ እና ከአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ የተለያዩ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ለህዝብ የማስተዋወቅ ሥራ ተሰርቷል፡፡

በዚሁ   መሠረት ከተለያዩ የውጭ አቅራቢ ድርጅቶች ጋር ቀጣይ ግንኙነቶችን ማድረግ የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ እነዚህ አቅራቢ ድርጅቶችም ኢትዮ-አግሮ ሴፍቲ ኃ/የተ/የግ/ማ የሻይ ምርት ማዘጋጃና ማቀነባበሪያ ፋብሪካ፣ ሊዩስ የምግብ ዘይትና አኩሪ አተር ምርቶች፣ ጭላሎ ምግብ ኮምፕሌክስ ሲሆኑ በቀጣይ አብሮ ለመሥራት የሚያስችል ቅድመ ትውውቅ ሥራ ተሠርቷል፡፡