የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የኢፌዴሪ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በየዘርፈቸው ለሚያከናውኗቸውና የየተቋማቱን የሥራ አፈጻጸም ለማገልበት የሚረዱ መልካም ተሞክሮዎችንና ከምርትና ገበያ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ጥቅምት 11 ቀን 2012 ዓ/ም በኢንሥኮ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡

በስምምነቱ ተቋማቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን የግብይት ዋጋዎችን እንዲሁም በመረጃዎች ላይ ተመሥርተው የተሚካሄዱ ጥናትና ጥናቶችንና ትንታኔዎችን ውጤቶች በመለዋወጥ በግብርናው ዘርፍ የሚሰሩ አካላትንና የአምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ መሆኑ በሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በዋነኝነት የአነስተኛ አርሶ አደሮችን የማምረት አቅም ለማጎልበት የሚያስችሉ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ድጋፎችን የማድረግ፣ በመረጃ ትንተና እና ጂአይኤስ ዙሪያ መልካ ተሞክሮዎች ከግብርና ትራንስፎርሜሽን የማግኘት እንዲሁም ከኤጀንሲው ጋር በመሆን የግብርና መረጃጃ አያያዝን የማዘመን ሥራዎችን ማከናወን የሚችልበት ዕድል እንደሚፈጥርለት ተገልጿል፡፡

በተመሣሣይም የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በመረጃ በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውጤቶችን ለማግኘት የሚያስችሉ ወቅታዊ የመረጃ ግብዓቶችንና በኢንሥኮ የተተገበሩ የመረጃ አያያዝ መልካም ተሞክሮዎችን የሚያገኝባቸውን ስልቶች መተግበር የስምምነቱ አካል መሆናቸው ታውቋል፡፡

አነስተኛ አርሶ አደሮችም በወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎች ላይ ተመስርተው ከሚነደፉ ስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎችና ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ እንደሚሆን በስምምነቱ ሰነዱ ተመልክቷል፡፡