ሀገሪቱ ፖለቲካ ስልጣን የበላይ የሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤትና በቅርንጫፍ የንግድ ግብይት ማእከላትበአካል በመገኘት የኮርፖሬሽኑን አጠቃላይ የንግድእንቅስቃሴ ገምግመዋል፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በአቶ መንግስቱ ከበደ ስለ ኮርፖሬሽኑ አመሠራረት፣ አደረጃጀት እና አሠራር እንዲሁም ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት በተመለከተ ሰፊ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን አያይዘውም በአሁኑ ጊዜ ኮርፖሬሽኑን በአሠራርና በአገልግሎት አሰጥጥ ያጋጡሙትን መሠረታዊ ችግሮች አስመልክቶ በቀድሞው አለ በጅምላ ላይ የነበሩ የአሰራር ችግሮች እንዲሁም የእህል መጋዘኖችን ለማስፋፋት የመሬት ጥያቄ በተመለከተ የአዳማ መጋዘን ርክክብ መጓተት እና የከተማ አስተዳደሩ ምላሽ መዘግየት ኮርፖሬሽኑ ውጤታማና ትርፋማ እንዳይሆን ዋና ችግሮች እንደሆኑ ለቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በቅድሚያ አስረድተዋል፡፡

የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እህልና ቡና፣ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ሥራዎች እንዲሁም በግዥና ማማከር የአገልግሎት ዘርፎችን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡ የኮርፖሬሽኑን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትና የንግድ ትስስር ሥራዎችን በተመለከተ የፎቶ አውደ ርዕይ በፎቶ መስኮት፣ የተለያዩ የሥራ ክፍሎችን እንቅስቃሴና የውጤት ተኮር አሠራር አተገባበርና ያስገኘው ውጤት በተመለከተ ከኃላፊዎችና ባለሙያዎች ገለጻ የተሰጣቸው ሲሆን፤ መስተካከል በሚገባቸው ጉዳዮች ዙሪያ አስተያየት በመስጠት ክፍተቶች እንዲታረሙ አሳስበዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ኮርፖሬሽኑ በግዢና ማማከር አገልግሎት ዘርፍ የሚሠራቸውን ሥራዎች አስመልክቶ በአዲስ አበባና በእህልና ቡናና በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ለገበያ ማረጋጊያና ለወጭ ንግድ የሚላኩ የግብርና ምርቶችን ማቀነባበሪያ ማደራጃና ማከማቻ ማዕከላትን የፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ሥራ ቃሊቲ መደብር እንዲሁም የአዳማ ቅርንጫፍ የግብይት ማዕከላትን ጎብኝተዋል፡፡ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱም ኮርፖሬሽኑ በአዳማ ቅርንጫፍ የግብይት ማዕከል የሀገር ውስጥ ገበያን ለማረጋጋት ለሀገር ውስጥ ገበያ ማረጋጊያ የሚደራጁ ምግብ ስብሎችንና ለዓለም ገበያ የሚቀርበው የቦሎቄ ምርት ጥራትን ለማስጠበቅየሚከናወኑ የእህል ጥራት ማስጠበቂያ መሣሪዎች አጠቃቀምን በመስክ ምልከታው ጎብኝተዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ዘውዱ የኮርፖሬሽኑን የዕቅድ አፈጻጸም በመስክ ጉብኝት ለማረጋገጥ ባስቀመጠው መመዘኛ (መገምገሚያ) መስፈርት መሠረት የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2009 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሙን መሠረት በማድረግ በሰጠው የዕቅድ ግምገማ ግብረመልስ መሠረት ኮርፖሬሽኑ ከሚጠበቀው በላይ ውጤታማ አፈጻጸም በማስመዝገቡ ከፍተኛ እርካታ እንዳገኙ ገልጸው ቋሚ ኮሚቴው የያዘውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ማሳካቱን ተናግረዋል፡፡

ሌሎች የቋሚ ኮሚቴ አባላትም በተመሳሳይ ዕቅዱና አፈጻጸሙ የተጣጣመ እንደሆነ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መንግሥቱ ከበደ የኮርፖሬሽኑ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ የፍጆታ ዕቃዎች ንግድ ሥራ የአዳማ ቅርንጫፍ ለመክፈት ያጋጠሙ አስተዳደራዊ ችግሮች እንዲሁም የእህል መጋዘኖችን ለማስፋፋት የመሬት ጥያቄና የከተማ አስተዳደር ምላሽ መዘግየትና የመሳሰሉት መሠረታዊ ችግሮችን በመቅረፍ በኩል በተለይ በውጭ ንግዱ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ያሉ ችግሮችን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴና የአዳማ ከተማ አስተዳደር በመተባበር ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡