የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የኢፌዴሪ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በየዘርፈቸው ለሚያከናውኗቸውና የየተቋማቱን የሥራ አፈጻጸም ለማገልበት የሚረዱ መልካም ተሞክሮዎችንና ከምርትና ገበያ ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ለመለዋወጥ የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ጥቅምት 11 ቀን 2012 ዓ/ም በኢንሥኮ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡
በስምምነቱ ተቋማቱ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን የግብይት ዋጋዎችን እንዲሁም በመረጃዎች ላይ ተመሥርተው የተሚካሄዱ ጥናትና ጥናቶችንና ትንታኔዎችን ውጤቶች በመለዋወጥ በግብርናው ዘርፍ የሚሰሩ አካላትንና የአምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ መሆኑ በሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ የንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በዋነኝነት የአነስተኛ አርሶ አደሮችን የማምረት አቅም ለማጎልበት የሚያስችሉ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ድጋፎችን የማድረግ፣ በመረጃ ትንተና እና ጂአይኤስ ዙሪያ መልካ ተሞክሮዎች ከግብርና ትራንስፎርሜሽን የማግኘት እንዲሁም ከኤጀንሲው ጋር በመሆን የግብርና መረጃጃ አያያዝን የማዘመን ሥራዎችን ማከናወን የሚችልበት ዕድል እንደሚፈጥርለት ተገልጿል፡፡
በተመሣሣይም የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ በመረጃ በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውጤቶችን ለማግኘት የሚያስችሉ ወቅታዊ የመረጃ ግብዓቶችንና በኢንሥኮ የተተገበሩ የመረጃ አያያዝ መልካም ተሞክሮዎችን የሚያገኝባቸውን ስልቶች መተግበር የስምምነቱ አካል መሆናቸው ታውቋል፡፡
አነስተኛ አርሶ አደሮችም በወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎች ላይ ተመስርተው ከሚነደፉ ስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎችና ፕሮጀክቶች ተጠቃሚ እንደሚሆን በስምምነቱ ሰነዱ ተመልክቷል፡፡
ደን ህይወት ነው፡፡ አዎ በእርግጥም ደን ህይወት ነው፡፡ ዓለማችንን እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥ መንስኤው የደን መመናመን ነው፡፡ ምድራችን ያለደን ውበት የላትም፡፡ ደን ስትለብስ ግን ግርማ ሞገሷን ትላበሳለች፤ እስትንፋሷም ይስተካከላል፡፡
ዕጽዋት የከተማችንን የአየር ንብረት ለመጠበቅም ሆነ አካባቢን ለማስዋብ ያላቸው ጠቀሜታ የጎላ ከመሆኑ አንጻር ችግኞችን መትከል የተተከሉትን ተንከባክቦ ማሳደግ ለአካባቢ ጥበቃ መሠረት ነው፡፡ በያዝነው በጀት አመት “አረንጓዴ አሻራ እናሳርፍ፤ በአንድ ጀምበር 200 ሚሊየን ችግኝ እንትከል!” በሚል መሪ ቃል በመላ ሀገሪቱ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል ያሳተፈ የችግኝ ተከላ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ መርኃ ግብሩ በዋናነት ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ/ም የሚከናወን ሲሆን እንቅስቃሴው ቀድሞ ተጀምሯል፡፡ ይህ መርኃ ግብር የሀገሪቱን የደን ሽፋን ትርጉም ባለው መልኩ አንድ እርምጃ ወደ ፊት የሚያራምድ መሆኑ በብዙዎች ተስፋ ተጥሎበታል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ይህንን ሀገራዊ አጀንዳ ተቀብለው ሀምሌ 6 ቀን 2011 ዓ/ም ሳሪስ በሚገኘው የኮርፖሬሽኑ የእህል ማከማቻ ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አካሂደዋል፡፡
በችግኝ ተከላው ወቅት የኮርፖሬሽኑ ኮርፖሬት ሰርቪስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታሪኩ በራሱ መርሃ ግብሩን አስመልክተው ደን ከሰው ልጆች ህይወት ጋር ቀጥተኛ ትስስር ያለውና ከደማችን ጋር የተያያዘ መሆኑን በመጥቀስ ንጹህና ያልተራቆተ አካባቢን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ያሳሰቡ ሲሆን ችግኞችን መትክል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትም እንዲጸድቁ ተገቢውን እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ በመጠቆም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ በአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራሙ የችግኝ ተከላን በዋና መሥሪያ ቤቱና በክልል የግብይት ማዕከላት የነደፈ ሲሆን የኮርፖሬሽኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የአካባቢ ፕሮግራሙን ተግባራዊ ማድረግ ከጀመሩ ዓመታትን አስቆጥረዋል፡፡
ዘንድሮም የተሣተፉት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በዕለቱ የተተከሉትን ችግኞችም ሆነ የቀደሙትን ተንከባክበው ለፍሬ እንደሚያበቁ በችግኝ ተከላ ፕሮግራሙ ላይ ቃል ገብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከሚያዚያ4-7/2011 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው 1ኛው አለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ፎረም እና የንግድ ትርዒት ባዛር ተሳትፎው በሁሉም ንግድ ሥራ ዘርፎች የሚቀርቡ ምርትና አገልግሎቶችን ለጎብኝዎች ማቅረብ ተችሏል፡፡ አንድ የንግድ ተቋምን ለማሳደግና በተሻለ ሁኔታ ቢዝነሱን ለማከናወን እንዲችል የገበያ ልማት ሥራ መሥራት በጣም ወሳኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ስለኮርፖሬሽኑ ጠቃሚ መረጃ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
ለሸማች ማህበራት፣ ለአርሶ አደሮች፣ ለጅምላ አከፋፋዮች፣ ለቸርቻሪዎች፣ ለኢንቬስተሮችና ለውጭ ሃገር ተሳታፊዎች ኮርፖሬሽኑን ማስተዋወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በንግድ ትርዒቱ በኮርፖሬሽኑ በተዘጋጀው የቡና ጠጡ ፕሮግራም ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመጋበዝ ኮርፖሬሽኑ ስለተቋቋመበት አላማና በኮርፖሬሽኑ ስለሚቀርቡ ምርትና አገልግሎቶች ዝርዝር ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡
የተለያዩ የሚዲያ አካላት ስለኮርፖሬሽኑ ዝርዝር መረጃ በአካል ተገኝተው በመጎብኘትና ሰራተኞችን ቃለ-መጠይቅ በማድረግ ልዩ ትኩረት ሰጥተውታል፡፡ የጎብኚዎችን ግብረ መልስ በተመለከተ በተለይ የፍጆታ እቃዎች ለምሳሌ ከውጪ የሚገቡ የዘይት ምርቶች በንግድ ትርዒቶች ላይ ለሽያጭ የሚቀርቡበት ዕድል ቢኖር፤ በፍጆታ እቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ የሚሠጠው አገልግሎት ለተቋማትና ቲን ቁጥር/ፈቃድ ላላቸው ብቻ የሚከናወን በመሆኑ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የማያደርግ ስለሆነ ይህ አሰራር ቢቀየር፤ እንዲሁም በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ በኩል የሚሸጡ ምርቶች የሚሸጡበት ዋጋ ዙሪያ ማስተካከያ ቢደረግ የሚሉ አስተያየቶችና ግብረ መልሶች ተወስደዋል፡፡