DSC_01.JPG

ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓም በቀድሞው ግሎባል በአሁኑ የኢትዮጵያ ሆቴል በተካሄደው የምስጋና ዕውቅና መርሃ ግብር ኮርፖሬሽኑ በ2015 ዓ/ም በተካሄደው 8ኛው የካይዘን ዓመታዊ የሽልማት ውድድር በካይዘን ትግበራና ውጤታማነት በአገልግሎት ዘርፍ 3ኛ ደረጃ ተሸላሚ፤ አቢሲኒያ የጥራት ሽልማት ድርጅት ባካሄደው ዓመታዊ የጥራት ውድድር በአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ ዘመናዊ አሠራር በመዘርጋት፣ የላቀና ተጨባጭ ዕድገት በማስመዝገብ እንዲሁም መልካም ስምን ጠብቆ ለአመታት በትጋት በመዝለቅ የወርቅ ዋንጫ ተሸላሚ ላደረጉ ሠራተኞችና አመራሮች የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቷል፡፡

የኮርፖሬሽኑ የህግ፣ ማህበራዊ ጉዳዮችና አሠራር ማሻሻያ ም/ዋ/ሥ/አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ይርጋሸዋ ተሾመ በመርኃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ኢንሥኮ ካይዘንን በተቋም ደረጃ ከተገበረበት ጊዜ አንስቶ አሠራሩን ከፍልስፍና ባለፈ በሁሉም ሠራተኛ ዘንድ ሰርጾ እንደ አንድ መሳሪያ ጥቅም ላይ መዋል መጀመሩን አስረድተው በዚህም በተጨማሪ ገቢ፣ የሥራ ቦታና ወጪ ቅነሳ አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ኮርፖሬሽኑ በካይዘን ትግበራ ለደረሰበት ስኬት ብሎም በአገልግሎት ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ ላገኘው ዕውቅና የኢትዮጵያ ካይዘን ልቀት ማዕከል ከአመራሩ ጀምሮ ባለሙያዎችን በማሠልጠንና አማካሪዎችን በመመደብ ያደረገው ክትትል ዓይነተኛ ሚና መጫውቱን አውስተው፤ በቀጣይም ሁሉም አካላት የተገኙ ውጤቶችን በሁሉም ዘርፍ፣ የሥራ ክፍሎችና ማዕከላት ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በተመሣሣይም የኮርፖሬሽኑ የአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ በአቢሲኒያ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ ምርትን ለበርካታ ዓመታት ለህብረተሰቡ በጥራት በማቅረብ፣ አሠራን በማዘመን፣ በታማኝነትና በሌሎችም የላቁ አሠራሮች በውጤታማ አመራር ሰጪነትና በሠራተኛው ትጉህ እቅስቃሴ ለወርቅ ዋንጫ፣ ሜዳሊያና ኒሻን ሽልማት በመብቃቱ የተሰማቸውን ደስታና በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የኮርፖሬሽኑ ተልዕኮ ህብረተሰብን ማገልገል ከመሆኑ አኳያ የተገኘው ሽልማትና ዕውቅና ይህን ዓላማ ለማሳካት እንደ መስፈንጠሪያ ሆኖ ሊያገለግል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በመድረኩ ላይ ኮርፖሬሽኑ ተሸላሚ በሆነባቸው መስኮች የተከናወኑ አበይት ተግባራትና የሽልማቶቹ የተገኙባቸውን ሂደቶች የተመለከቱ መረጃዎች የቀረቡ ሲሆን፤ ለካይዘን የልቀት ማዕከል እና የአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ ላገኘው ዕውቅናና ሽልማት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫና አመራር በመስጠት አስተዋጽዖ ላበረከቱ የንግድ ሥራ ዘርፎችና ለኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የምስጋና ሽልማቶች ተበርክተዋል፡፡

በመርኃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የኮርፖሬሽና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ የተገኘው ውጤት የተቋሙን ዓላማ ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ የሚተጉ አመራና ሠራተኞች ውጤት መሆኑን ገልጸው፤ የተገኘው ውጤት በቀጣይ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል አመላካች መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የደንበኞችን እርካታ ጥራቱ በጠበቀ አገልግሎትና ምርት አቅርቦት እንዲሁም ተደራሽነት ማጎልበት እንደሚገባ፤ ለዚህም የፈጸሚን የመፈጸም አቅም ለማጎልበት ሥራን የያሳልጡ፣ ወጪ ቆጣቢ፣ ብክነትን የሚከላከሉና የተሻሻሉ የሥራ ማሳለጫ መሣሪያዎችን በሥፋት ሥራ ላይ የማዋሉ ተግባር ሊጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

 ተጨማሪ ምስሎችን እዚህ ማየት ይችላሉ፡፡

 

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ!
ድረገጽ፡- https://www.etbc-ethiopia.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo
ዜና ኢንሥኮ አንድሮይድ መተግበሪያ፡- https://t.ly/DiXR
ዩትዩብ ቻነል፡- https://www.youtube.com/@etbcinfocom4858
አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ያድርሱን፡፡
ኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ የ 57ሺ ኩንታል የጃፓን ሩዝ ድጋፍ አደረገ፡፡ የምግብ ድጋፍ ርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ግንቦት 08/ 2015 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ እቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ ቃሊቲ ሽያጭ ማእከል የተካሄደ ሲሆን የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው፣ በገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስታት ትብብር ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ግርማ፣ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

 

ሰመሪታ ሰዋሰው የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በድጋፍ ርክክቡ ወቅት ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያና ጃፓን የቆየ የኢኮኖሚ ትብብር እንዳላቸው ጠቅሰው በጃፓን መንግስት የተደረገው የምግብ ድጋፍ የሀገራቱን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የተደረገው የ57 ሺ ኩንታል የሩዝ ምግብ ድጋፍ 300 ሚሊየን ብር እንደሚገመት ጠቁመዋል፡፡

 

ኢቶ ታካኮ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ባስተላለፉት መልእክት የርክክብ ሥነ-ሥርዓቱን ላስተባበሩት የገንዘብ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን መንግስታቸው የኢትዮጵያን ህዝብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚያግዝ ተከታታይነት ያለው ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ አክለውም ድጋፉ በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በኩል ለኅብረተሰቡ በተቻለ ፍጥነት እንደሚሰራጭ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

 

አቶ ቶውፊቅ ይመር በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ እቃዎች ን/ስ/ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ በምግብ ድጋፍ ርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ላይ ለተገኙት እንግዶችና የሚዲያ አካላት በፍጆታ እቃዎች ን/ስ/ ዘርፍ የቃሊቲ ሽያጭ ማእከልን ያስጎበኙና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ የምግብ ድጋፉን በአግባቡ ለህብረተሰቡ ለማሰራጨት የሚያስችል አቅምና ልምድ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር መጠነኛ የሆነ የመሸጫ ተመን እንደሚወጣለት ገልጸው፣ በሸማች ህብረት ስራ ማኅበራት በኩል ለኅብረተሰቡ እንደሚደርስ ጠቁመዋል፡፡

 

Japan_2.jpg

Japan_4.jpg

 

ኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከአራቱም ዘርፎችና ከዋና መ/ቤት የተውጣጡ ሴት ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በአንድነት ፓርክ መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ/ም ጉብኝት አካሂደዋል፡፡

ጉብኝቱን ያዘጋጀውና ያስተባበረው የኮርፖሬት ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት አለማየሁ ከየዘርፉና ከዋና መ/ቤት የተወከሉ ሴት ሰራተኞች በጉብኝቱ መሳተፋቸውን ገልጸው በስራቸው የበለጠ ውጤታማ እና ጠንካራ እንዲሆኑ ለማገዝ በጽ/ቤቱ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አክለውም ኮርፖሬሽኑ የዘንድሮውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በጉብኝት እያከበረ መሆኑን ጠቅሰው ይህም በየዘርፉና በዋና መ/ቤት ያሉ ሴት ሰራተኞችን ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እንደሚረዳ ተናግረዋል፡፡

በጉብኝቱ የተሳተፉና ያነጋገርናቸው ሰራተኞች በአንድነት ፓርክ በመገኘት የሀገራቸውን ታሪክና የተፈጥሮ ሃብት በመመልከታቸውና በአጠቃላይ በጉብኝቱ መዘጋጀት የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡

March_8_DSC_7441.JPG

 


አዳዲስና ዘመናዊ አሰራር ለዘረጉ፣ የላቀና ተጨባጭ እድገት ላስመዘገቡ፣ መልካም ስማቸውን ጠብቀው ለአመታት በትጋት ለዘለቁ ተቋማት /MILESTONE, BRANDING AND REPUTATION/ አቢሲኒያ የጥራት ድርጅት እውቅና ለመስጠት ሚያዚያ 1 ቀን 2015 ዓ/ም በኢንተርሊግዠሪ ሆቴል (በቀድሞ ኢንተርኮንቲኔታል ሆቴል) ባዘጋጀው የኢንደስትሪ ሽልማት መርሃ-ግብር ላይ በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ሥራ ዘርፍ /ኢትፍሩት/ የከፍተኛ ክብር ሽልማት የወርቅ ዋንጫ፣ የወርቅ ሜዳሊያና የከፍተኛ ክብር ዲፕሎማ ተሸላሚ ሆኗል፡፡

ለዘርፉ ስራ አርዓያ የሆኑ አምስት ምርጥ ሰራተኞች የወርቅ ሜዳሊያ ሽልማት ሲሸለሙ፣ የመካከለኛ ደረጃ ሁለት አመራሮች ደግሞ የኒሻን ተሸላሚ ሆነዋል፤ እንዲሁም የዘርፉ ስራ አስፈጻሚ የከፍተኛ ክብር (የኮርዶን) ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

ይህ በሀገራችን በኢንዱስትሪው ዘርፍ የተካሄደ የመጀመሪያው የሽልማት መርሀ ግብር ሲሆን ከ57ሺህ የኢንዱስትሪ ተቋማት የተመረጡት 50 ብቻ ሲሆኑ በአጠቃላይ ተቋማዊ ውጤታቸው ላይ ከ2009-2014 በተደረገ ውጫዊ ምዘና በ24 መሰረታዊ መለኪያዎች ላይ ተመስርቶ በተገኘ ውጤት እንዲመረጡና እንዲሸለሙ መደረጉን በሽልማት መርሃ -ግብሩ ወቅት ተገልጿል፡፡
በዚህ የሽልማት ፕሮግራም ላይ የኮርፖሬሽኑ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሃሰን መሃመድ፣ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ እና የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮችና ዳይሬክተሮች እንዲሁም በዘርፉ ጥሪ የተደረገላቸው የዘርፉ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

ዘርፉ ይህንን ከፍተኛ ሽልማት ያገኘው በኮርፖሬሽኑ የስራ አመራር ቦርድ እና የኮርፖሬሽኑ ማኔጅመንት በሚሰጠው ስትራቴጂካዊ አመራር በመመራት፣ የዘርፉ ማናጅመንትና ሠራተኞች ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት እንዲሁም ሌሎች ዘርፎች ባደረጉት እገዛና ድጋፍ በመሆኑ ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ፤ ደስ አለን እያለ፣ ዘርፉ ይህንን ስኬት እንዲያስመዘግብ ድጋፍና እገዛ ላደረጉ የኮርፖሬሽኑ ቤተሰቦችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ ምስጋና ያቀርባል፡፡

የአትክልትና ፍራፍሬ ንግድ ስራ ዘርፍ ለበርካታ ዓመታት ትኩስና ጥራታቸውን የጠበቁ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለሃገር ውስጥና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ይታወቃል፡፡

 

 

 

 

Vegetable_Oil.jpg

የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በአገራችን ያለውን መሠረታዊ የምግብ ፍጆታ ምርቶች አቅርቦት እጥረትና የዋጋ ንረትን ለመቋቋም የተለያዩ የፍጆታ ምርቶችን በማከፋፈል ገበያውን ማረጋጋት እና የሃገር ውስጥ አምራቾችን ማበረታታት ከተሰጡት ተልዕኮዎች መካከል ተጠቃሽ ናቸው፡፡

በመሆኑም ኮርፖሬሽኑ ከፊቤላ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማህበር የ26 ሺህ ሊትር የሱፍ የምግብ ዘይት ግዢ በመፈጸም ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ ውስጥ 6 ሺህ ሊትር በኮርፖሬሽኑ የአትክልትና ፍራፍሬ ሱቆች በኩል ለህብረተሰቡ ፍጆታ እንዲውል የተደረገ ሲሆን ቀሪው 20 ሺህ ሊትር ደግሞ በቅርቡ የሚሰራጭ ይሆናል፡፡ ባለ አምስት ሊትር የሱፍ የምግብ ዘይቱ በ930 ብር በአዲስ አበባ እና በክልሎች እየተሸጠ ሲሆን ይህም ገበያ ላይ ካለው ዋጋ ጋር ሲነጻጸር 13 በመቶ ያህል ቅናሽ ያለው ነው፡፡